በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

6ኛው ቁልፍ፦ ይቅር ባይነት

6ኛው ቁልፍ፦ ይቅር ባይነት

6ኛው ቁልፍ፦ ይቅር ባይነት

“እርስ በርስ መቻቻላችሁንና እርስ በርስ በነፃ ይቅር መባባላችሁን ቀጥሉ።”—ቆላስይስ 3:13

ምን ማለት ነው? የተሳካ ትዳር ያላቸው ባልና ሚስት ካለፈው ስህተታቸው የሚማሩ ቢሆንም ያለፈውን ሁሉ እያስታወሱ “ማርፈድ እንደሆነ ልማድሽ ነው” ወይም “መቼም ቢሆን አትሰማም” እንደሚሉት ያሉ የተጋነኑ አነጋገሮችን አይጠቀሙም። ባልም ሆነ ሚስት ‘በደልን ንቆ መተው መከበሪያ ነው’ የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌ ያስታውሳሉ።—ምሳሌ 19:11

አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? አምላክ ‘ይቅር ለማለት ዝግጁ’ ነው፤ ሰዎች ግን አብዛኛውን ጊዜ እንደ አምላክ ይቅር ባዮች አይደሉም። (መዝሙር 86:5 NW) እልባት ሳይበጅላቸው የቀሩ ተደራራቢ በደሎች ተጠራቅመው ይቅር ማለት አስቸጋሪ የሚመስልበት ደረጃ ላይ ይደርሳሉ። ይህም ሁለቱም ስሜታቸውን አውጥተው መናገር እንዲከብዳቸውና አንዳቸው ለሌላው ስሜት ደንታ ቢስ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። እንዲሁም ሁለቱም ፍቅር በሌለበት ትዳር ውስጥ የግዳቸውን እየኖሩ እንዳሉ እንዲሰማቸው ያደርጋል።

ይህን ለማድረግ ሞክር፦ የሠርጋችሁ ሰሞን ወይም ለጋብቻ በምትጠናኑበት ወቅት የተነሳችኋቸውን ፎቶግራፎች ተመልከት። ችግሮች ተነስተው አመለካከትህ ከመለወጡ በፊት የነበረህን ፍቅር ለማደስ ጥረት አድርግ። ከትዳር ጓደኛህ ጋር ስትተዋወቁ በዚያን ጊዜ የማረከህ ባሕርይ ምን እንደነበር አስብ።

አሁንስ ከትዳር ጓደኛህ በጣም የምታደንቀው ባሕርይ ምንድን ነው?

ይበልጥ ይቅር ባይ መሆንህ በልጆቻችሁ ላይ ስለሚያሳድረው በጎ ተጽዕኖ አስብ።

ቁርጥ ውሳኔ አድርግ። ከትዳር ጓደኛህ ጋር አለመግባባት ሲፈጠር ቀደም ሲል የተሰማህን ቅሬታ አሁን ላለማንሳት ማድረግ ስለምትችላቸው አንድ ወይም ሁለት ነገሮች አስብ።

ለትዳር ጓደኛህ የትኛውን ባሕርይዋን እንደምታደንቅላት ጠቅሰህ ለምን አታመሰግናትም?—ምሳሌ 31:28, 29

ከልጆቻችሁ ጋር ባለህ ግንኙነት ይቅር ባይ መሆንህን የምታሳይባቸውን አንዳንድ መንገዶች አስብ።

ይቅር ባይ መሆን እያንዳንዱን የቤተሰብ አባል እንዴት እንደሚጠቅመው ከልጆቻችሁ ጋር ለምን አትወያዩበትም?

[በገጽ 8 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

ይቅር ስትሉ ዕዳውን ሰረዛችሁ ማለት ነው፤ የሰረዛችሁትን ዕዳ እንደገና መጠየቅ አትችሉም